ጊዜያዊ የረጅም ጊዜ  (የኮንትራት) ቅጥር ማስታወቂያ

0
12

 

 

ቁጥር የሠ/ኮ.ቅ.ማ/3148/2018

                                                                                                                                                                                         ቀን 13/09/2018 ዓ/ም

 

የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ከዚህ በታች ባለው ክፍት የስራ መደብ ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታውን ከሚያሟሉ ስራ ፈላጊዎች መካከል በጊዜያዊ የረጅም ጊዜ  (በኮንትራት) ቅጥር አወዳድሮ በመቅጠር ማሰራት ይፈልጋል፡፡

 

ተቁ የሥራ መደቡ መጠሪያ ደረጃ የመ/መ/ቁ ደመወዝ ብዛት የሥራ ቦታ ተፈላጊ የትምህርት ዝግጅት ተፈላጊ የስራ ልምድ
1. የግዢ ባለሙያ 2

 

IX አሚ-1684 በኮርፖሬሽኑ የደመወዝ ስኬል መሠረት 01 አዲስ አበባ ቅርንጫፍ በግዢና የአቅርቦት ሰንሰለት፣ ስራ አመራር፣ በኢኮኖሚክስ፣ በህዝብ አስተዳደር፣ በቢዝነስ አስተዳደርና በተዛማጅ የትምህርት መስክ ·  የመጀመሪያ ድግሪ 1 ዓመት አግባብ ያለው የስራ ልምድ

 

ማሳሰቢያ፡-

  • የምዝገባ ቀን ማስታወቂያው በበኩር ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን  ጀምሮ ለ5 ተከታታይ የስራ ቀናት ይሆናል፡፡
  • አመልካቾች ለፈተና በሚቀርቡበት ጊዜ ማንነታቸውን የሚገልፅ መታወቂያ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  • አመልካቾች በእምነት ማጉደል፣ በማጭበርበር ወይም በስርቆት ወንጀል ተከሰዉ ስልጣን ባለዉ አካል ተፈርዶባቸዉ የመቀጠር መብታቸዉን እንዲጠቀሙ ስልጣን ያለዉ ፍርድ ቤት የወሰነበትን ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  • አመልካቾች ለፈተና በሚቀርቡበት ጊዜ ኦርጅናሉን የትምህርትና የስራ ልምድ ለተጠየቀበት መደብ ብቻ የስራ ልምዳቸውን መረጃ ኦርጅናል ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  • ከተጠቀሰዉ አግባብነት ያለው የትምህርት ዝግጅት እና የስራ ልምድ ውጭ ለምዝገባ የሚቀርቡ ሌሎች ማስረጃዎች ተቀባይነት አይኖራቸዉም፡፡
  • አመልካቾች መልካም ስነ-ምግባር ያላቸው፣ ከማንኛውም ደባል ሱስ የፀዱ፣ጥሩ ስብዕና ያላቸው፡፡
  • ተወዳዳሪዎች በተመዘገቡበት የስራ መደብ ለምን ተቀጥረው መስራት እንደፈለጉ በጽሁፍ ገልፀው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  • አመልካቾች የሙያ ብቃት በሚያስፈልጋቸው የትምህርት ዝግጅት የብቃት ማረጋገጫ በማስታወቂያው በተጠየቀው የትምህርት ደረጃ ልክ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  • የሙያ ብቃት ምዘና ያልተጀመረባቸው የትምህርት መስኮች ከሚመለከተው ተቋም የሙያ ብቃት አለመጀመሩን ማስረጃ ካቀረቡ መመዝገብ ይችላሉ፡፡
  • የኮንትራት ቅጥሩ ለ6 ወር ሆኖ እንደአስፈላጊነቱ በየ6 ወሩ ይታደሳል፡፡
  • በግል ተቋማት የተሰራባቸው የስራ ልምዶች የሰራ ግብር የተከፈለበት ማስረጃ ከገቢዎች ጽ/ቤት ማቅረብ ይገባል፡፡
  • ተወዳድረው ያለፍ የስራ ተያዥ ወይም ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  • ፈተና የሚሰጥበት ቀንና ቦታ በሌላ ማስታወቂያ ይገለፃል፡፡
  • አመልካቾች የምትመዘገቡበት ሊንክ በዌብሳይታችን ameco.et ማግኘት ትችላላችሁ ወይም ይህ ሊንክ በመጫን ይመዝገቡ https://forms.gle/DmxUASmvKoQqxCbF9 መመዝገብ የሚችሉ መሆኑን እናሳስባለን፡፡
  • ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058 226 5007 ባህር ዳር ይደዉሉ፡፡

የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

ባሕር ዳር

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here