የፍ/ባለመብት በፀደይ ሆቴል የሚጣል እቁብ ማህበር እና የፍ/ባለ እዳ ታደሰ ገሠሠ መካከል ስላለው የአፈጻጸም ክስ ጉዳይ፤ የባለእዳው ንብረት የሆነው እና በሽንዲ ከተማ ቀበሌ 01 ክልል ውስጥ ተመዝግቦ የሚገኘው ፤ በምስራቅ እና በምእራብ ሙሉቀን ቀርባህ፣ ፣በሰሜን መልሶ ተፈራ በደቡብ መንገድ ተዋስኖ የሚገኘው ቤት፤ የመነሻ ዋጋው በዜሮ ሆኖ፤ ግንቦት 19/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 3፡00 እስከ 6፡00 በግልጽ ጨረታ ይሸጣል፡፡ ስለዚህ በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ከላይ በተጠቀሰው ቦታና ሰአት በመገኘት መጫረት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፤ አሸናፊው እንደታወቀ የሽያጩን ገንዘብ ከተቻለ ሙሉውን፣ ካልተቻለ ¼ኛውን በምእራብ ጎጃም ዞን ከፍ/ፍ/ቤት በሞዴል 85 የሚያሲዙ መሆኑን እየገለጽን፤ ከላይ በአዋሳኝ የተጠቀሰው ቤት ከሕብረት ባንክ ብር 215‚000 (ሁለት መቶ አስራ አምስት ሽህ) እዳ ያለበት መሆኑን እንድታውቁት ፍ/ቤቱ አዝዟል፡፡
የምእራብ ጎጃም ዞን ከፍ/ፍ/ቤት

