በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በምስራቅ ደምቢያ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት አማካኝነት ለምስ/ደ/ወ/ አስተዳደር /ጽ/ቤት ለ3ኛ ፌዝ ለቢሮ ግንባታ አገልግሎት የሚውሉ የግንባታ ማቴሪያል ተጫራቾችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡
- በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸዉ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸዉና ተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸዉን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-2 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸዉን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዳቸዉ ጋር አያይዘዉ ማቅረብ አለባቸዉ፡፡
- የጨረታ ሰነድ ብር 300 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ሰነዱን መግዛት የምትፈልጉ ከግንቦት 17/2018 ዓ/ም ጀምሮ በምስራቅ ደምቢያ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 6 ዘወትር በሥራ ሰዓት መግዛት ይችላሉ፡፡
- የግንባታ ማቴሪያል ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሠነዱ ማግኘት የሚችሉ ሲሆን አሸናፊዉ የሚለየዉ በሎት ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በምስራቅ ደምቢያ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 6 ከግንቦት 17/2018 ዓ/ም እስከ ሰኔ 1/2018 ዓ/ም ባሉት ተከታታይ ቀናት መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ) ቦንድ ለሚወዳደሩበት ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒዩ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ደረሰኝ በፖስታ ታሽጎ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘዉ ማቅረብ አለባቸዉ ፡፡
- ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ሰኔ 2/2018 ዓ/ም በ3፡30 ታሽጎ በግዥ ንብረት አስተዳደር ቡድን መሪ ቢሮ ቁጥር 6 ሰኔ 2/2018 ዓ.ም በ4.00 ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ ባይገኙም ለጨረታዉ መሟላት የሚገባቸዉ ሁኔታዎች ከተሟሉ ተጫራቾች በሌሉበት ጽ/ቤቱ የጨረታዉን ፖስታ የመክፈት ስልጣን አለዉ፡፡
- ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታዉ ማሸነፈቸዉ እና የዉል ስምምነት እንዲፈጽሙ በተገለጸበት ጊዜ ካሸነፉበት ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ የዉል ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒዩ) ወይም በጥሬ ገንዘብ ደረሰኝ ማስያዝ እና ንብረቱን ምስ/ደ/ወ/ አሰተዳደር ንብረት ክፍል ገቢ ማድረግና የጫኝና አዉራጅ በተጫራቹ የሚሸፈን መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- የግንባታ ቁሳቁሱን የምንረከበዉ በላብራቶሪ ተፈትሾ ሲያልፍ ብቻ ነዉ፡፡
- ስለ ጨረታዉ ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 6 በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 335 0632 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
ማሳሰቢያ፡-ከዚህ በፊት በየትኛዉም ደረጃ በነበራቸዉ የአፈጻጸም ችግር ምክንያት የታገዱ አቅራቢዎችን አይመለከትም፡፡
የምስራቅ ደምቢያ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

