አፈ/ከሳሽ መ/ታ ኤፍሬም አለኸኝ እና በአፈ/ተከሳሽ እነ አንሙት የኔነህ መካከል ስለአለው የገንዘብ አፈፃፀም ክስ ክርክር ጉዳይ አፈፃፀም ተከሳሾች በፍርዱ መሰረት መፈፀም ባለመቻላቸው ምክንያት በቲሊሊ ከተማ 02 ቀበሌ በአዋሳኝ በምሥራቅ አዝመራው፣ በምዕራብ አየሁ መኮነን፣ በሰሜን መንገድ እንዲሁም በደቡብ አንሙት የኔነህ መካከል የሚገኝ በአቶ ቢሻው ሙሉጌታ ስም ተመዝግቦ የሚገኘውን ቤት መነሻ ዋጋውን ብር 1,773,615.77 (አንድ ሚሊዮን ሰባት መቶ ሰባ ሶስት ሺህ ስድስት መቶ አስራ አምስት ብር ከሰባ ሰባት ሳንቲም) በጫረታ ይሸጣል፡፡ የጨረታ ማስታወቂያው ሰኔ 01/2018 ዓ/ም እስከ ሀምሌ 01/2018 ዓ/ም በጋዜጣ ወጥቶ ቆይቶ ጨረታው ሀምሌ 02/2018 ዓ/ም ከረፋዱ 3፡00 እስከ 4፡00 ድረስ የሚከናውን ይሆናል፡፡
ማሳሰቢያ፡- ተጫራቾች የግምቱን ¼ ኛውን ገንዘብ ቀድመው (በሲፒኦ) አስይዘው በእለቱ መጫረት የሚችሉ መሆኑን ፍ/ቤቱ አዝዟል፡፡
የጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ ፍ/ ቤት

