በደቡብ ጎንደር አስተዳደር ዞን የጉና በጌ ምድር ወረዳ የክምር ድንጋይ መሪ ማዘጋጃ ቤት የከተማ ቦታ በሊዝ ስለመያዝ በሚደነግገው አዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀጽ 8 ንዑስ አንቀጽ 1 እና በሊዝ መመሪያ ቁጥር 1/2005 መሰረት 2018 በጀት ዓመት 1.ኛ ዙር በጨረታ ለመኖሪያ አገልግሎት 8 (ስምንት) ለድርጅት 1 (አንድ) ቦታዎችን ለተጫራቾች ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡
- መጫረት የሚፈልጉ ማንኛውም ሰው ወይም ድርጅት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) የሥራ ቀናት ከ2፡30 እስከ 11፡30 የማይመለስ ብር 400 (አራት መቶ ብር) በመክፈል ቢሮ ቁጥር 6 መግዛት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው የሚዘጋው በ10 ኛው ቀን በ11፡30 ይሆናል፡፡
- ጨረታው የሚከፈተው ከተዘጋበት ቀን ቀጥሎ ባለው የሥራ ቀን በ3፡00 ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በክምር ድንጋይ ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት አዳራሽ ይሆናል፡፡
- መስሪያ ቤቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ቦታውን ለመጎብኘት ከፈለጉ ከጨረታ ኮሚቴ ጋር መጎብኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ (ሲፒኦ) ለድርጅት 15 በመቶ እንዲሁም ለመኖሪያ 10 በመቶ ህጋዊ ከሆነ ባንክ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ በጽ/ቤቱ የውስጥ ማስታወቂያ ሰሌዳ ወይም በስልክ ቁጥር 09 18 71 44 11 ደውለው መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
የክምር ድንጋይ መሪ ማዘጋጃ ቤት

