የሐራጅ ጨረታ ማስታወቂያ

0
10

በአፈ/ከሳሽ አቶ ሽመልስ ውዴ እና በአፈ/ተከሳሾች 1. አቶ አበበ ሽፈራው፣ 2. አቶ ላቀው ዘውዱ፣ 3. አቶ ታምር እናውጋው መካከል ስላለው የገንዘብ የአፈጻጸም ክስ ክርክር ጉዳይ በዕድውሃ ከተማ  ቀበሌ 01 በምሥራቅ ደስታ ሙንየ፣ በምዕራብ ዋለ አባተ፣ በሰሜን ክፍት ቦታ እንዲሁም በደቡብ መንገድ የሚያዋስነው የ1ኛ ተከሳሽ ቤት በመነሻ ዋጋ ብር 1,425,656.25 (አንድ ሚሊዮን አራት መቶ ሀያ አምስት ሽህ ስድስት መቶ ሃምሳ ከሃያ ከአምስት ሳንቲም) በማድረግ ጨረታው ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 3፡00 እስከ 6፡00 ባለው ጊዜ ውስጥ በጨረታ ስለሚሸጥ መጫረት የሚፈልጉ ሁሉ በጨረታው ቀንና ሰዓት በቦታው በመገኘት መጫረት የሚችሉ ሲሆን የጨረታው አሸናፊ የአሸነፈበትን 1/4ኛውን በቀጠሮው ቀን የሚያስይዝ ሲሆን ስመ ንብረት ዝውውሩን በተመለከተ የጨረታው አሸናፊ የሚሸፍን መሆኑን አውቆ እንዲጫረት ሲል ፍርድ ቤቱ አዝዟል፡፡

የሸበል በረንታ ወረዳ ፍ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here