ፀደይ ባንክ አ.ማ ያበደረዉን ብድር መመለስ ያልቻሉ ደንበኞች ለብድሩ አመላለስ በመያዣ ያስያዛቸዉን ቤቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል:: በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ንብረቶች የተቀመጡትን ቅድመ ሁኔታዎችን እና ደንቦችን የምታሟሉ እንድትጫረቱ ይጋብዛል::
| ተ.ቁ | የተበዳሪ ስም | የንብረት አስያዥ ስም | የንብረቱ መገኛ ቦታ፣የካርታ ቁጥር እና የቦታው አገልግሎት | የቦታው ስፋት | የጨረታ መነሻ ግምት |
| 1 | አቶ መሀሪ ታምር ልመንህ | አቶ መሀሪ ታምር ልመንህ | ቁጭ ከተማ ቀበሌ 01 ካርታ ቁጥር 95/2010 የመኖሪያ ቤት አገልግሎት፡፡ | 200 ካ.ሜ 2 | 1‚675‚257.93 |
| 2 | አስቻለው ቀረብህ | አስቻለው ቀረብህ | ቡሬ ከተማ ቀበሌ 03 ካርታ ቁጥር 6931/2007 | 175 ካ.ሜ 2 | 711‚343.80 |
| 3 | ታደለ ጋሹ ሙሉነህ | ወልደየስ አስራደ ተሰራ | ቡሬ ከተማ ቀበሌ 01 ካርታ ቁጥር 6931/2007 | 250 ካ.ሜ | 811‚702.44 |
ተጫራቾች ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች
- ተጫራቾች የጨረታ መነሻ ዋጋ 1/ 4ኛውን በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ይዘዉ መቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ሲቀርቡ ማንነታቸዉን የሚገልጽ መታወቂያ ይዘዉ መቅረብ አለባቸዉ፡፡ ተጫራቹ ድርጅት ከሆነ የሚጫረተዉ ሰዉ ዉክልና የድርጅቱን መተዳደሪያ ደንብ እንዲሁም የድርጅቱን ህጋዊ ሰዉነት ያገኘበትን የምዝገባ የምስክር ወረቀት ይዞ መቅረብ አለበት፡፡
- ለመንግስት የሚከፈል ማንኛዉም ግብር ቫትን ጨምሮ ከቦታዉና ከቤቱ ጋር የተያያዘ ክፍያ እንዲሁም ስም ለማዞር የሚወጡ ወጭዎች በተጫራቾች ወይም በገዥ የሚሸፈን ይሆናል፡፡
- የጨረታው አሸናፊ የጨረታ ዉጤቱ በሚመለከተዉ አካል ፀድቆ አሸናፊነቱ በተረጋገጠ በ15 ቀን ዉስጥ ያሸነፈበትን ሙሉውን ገንዘብ ከፍሎ ማጠናቀቅና ቤቱን መረከብ ይኖርበታል፡፡
- የጨረታ አሸናፊዉ በ15 ቀን ዉስጥ ያሸነፈበትን ሙሉዉን ገንዘብ ገቢ ካላደረገ ያስያዘዉን ¼ኛውን ለባንኩ ገቢ ሆኖ ጨረታዉ እንደገና ይወጣል፡፡
- ጨረታዉ ነሀሴ 7 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 እሰከ 6፡00 በፍ/ሰላም ከተማ ከሚገኘዉ የፀደይ ባንክ ፍ/ሰላም ዲስትሪክት ግራዉድ ላይ ይሆናል፡፡
- ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ቤቶችን በባንኩ አማካኝነት መጎብኘት ይቻላል፡፡ ለበለጠ መረጃ 058 775 1154 ይደዉሉ፡፡
ፀደይ ባንክ ፍኖተ ሰሳም ዲስትሪክት

