የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ከዚህ በታች በተጠቀሰው ክፍት የስራ መደብ አስፈላጊዉን የትምህርት ዝግጅትና የስራ ልምድ ተፈላጊ ችሎታውን ከሚያሟሉ ስራ ፈላጊዎች መካከል ጊዚያዊ የረጅም ጊዜ /በኮንትራት / ቅጥር አወዳድሮ በመቅጠር ማሰራት ይፈልጋል፡፡
| ተቁ | የሥራ መደቡ መጠሪያ | ደረጃ | የመ/መ/ቁ | ደመወዝ | ብዛት | ዳይሬክቶሬት | የሥራ ቦታ | አግባብ ያለው የትምህርት ዝግጅት | አግባብ ያለው የስራ ልምድ |
| 1 | የድምጽ ባለሙያ /ኦዲዮ ኢንጅነር 1/ | 10 | አሚ-1611 | በኮርፖሬሽኑ የደመወዝ ስኬል መሰረት | 01 | አዲስ አበባ ሚዲያ ቴክኖሎጂ | አዲስ አበባ | በኤሌክትሪካል፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ኮምፒውተርና ኤሌክትሮ ሜካኒካል፣ በብሮድካት ምህንድስና እንዲሁም በመረጃና ኮሙንኬሽን ቴክኖሎጂ፣ በኤሌክትሮኒክስና ተግባቦት ቴክኖሎጂ፣ በኤሌክትሮኒክስ ተግባቦት ቴክኖሎጂ ስራ አመራር፣ ሲኒማቶግራፊ ፣ቪዲዮግራፊ ፣ ብሮድካስት ጋዜጠኝነት፣ ኦዲዮቪዲዮ ቴክኖሎጂ፣ ፎቶ ኢሜጅንግ፣ አርት ፔይንቲግ ወይም በተዛማጅ የትምህርት መስክ የሰለጠነ | የመጀመሪያ ዲግሪና 2 ዓመት አግባብነት ያለው የስራ ልምድ |
ማሳሰቢያ፡-
- የምዝገባ ቀን ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ5 ተከታታይ የሥራ ቀናት ይሆናል፡፡
- አመልካቾች ለፈተና በሚቀርቡበት ጊዜ ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- አመልካቾች በእምነት ማጉደል በማጭበርበር ወይም በስርቆት ወንጀል ተከሰዉ ስልጣን ባለዉ አካል ተፈርዶባቸዉ የመቀጠር መብታቸዉን እንዲጠቀሙ ስልጣን ያለዉ ፍርድ ቤት የወሰነበትን ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- አመልካቾች ለፈተና በሚቀርቡበት ጊዜ ኦርጅናሉን የትምህርትና የስራ ልምድ ለተጠየቀበት መደብ ብቻ የስራ ልምዳቸውን መረጃ ኦርጅናል ይዘዉ መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ከተጠቀሰዉ አግባብነት ያለው የትምህርት ዝግጅት እና የሥራ ልምድ ውጭ ለምዝገባ የሚቀርቡ ሌሎች ማስረጃዎች ተቀባይነት አይኖራቸዉም፡፡
- አመልካቾች መልካም ስነ-ምግባር ያለው/ላት ከማንኛውም ደባል ሱስ የፀዳ/ች እና ጥሩ ስብዕና ያለው/ላት፡፡
- ተወዳዳሪዎች በተመዘገቡበት የስራ መደብ ለምን ተቀጥረው መስራት እንደፈለጉ በጽሁፍ ገልፀው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- አመልካቾች የሙያ ብቃት በሚያስፈልጋቸው የትምህርት ዝግጅት የብቃት ማረጋገጫ በማስታወቂያው በተጠየቀው የትምህርት ደረጃ ልክ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የሙያ ብቃት ምዘና ያልተጀመረባቸው የትምህርት መስኮች ከሚመለከተው ተቋም የሙያ ብቃት አለመጀመሩን ማስረጃ ካቀረቡ መመዝገብ ይችላሉ፡፡
- የኮንትራት ቅጥሩ ለ6 ወር ሆኖ እንደአስፈላጊነቱ በየ6 ወሩ ይታደሳል፡፡
- ተወዳድሮ ያለፈ የስራ ተያዥ/ዋስ/ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
- ፈተና የሚሰጥበት ቀንና ቦታ በሌላ ማስታወቂያ ይገለፃል፡፡
- አመልካቾች የምትመዘገቡበት ሊንክ በዌብሳይታችን ameco.et ማግኘት ትችላላችሁ ወይም ይህ ሊንክ በመጫን ይመዝገቡ
https://forms.gle/wUye63btqpfmTR677 መመዝገብ የሚችሉ መሆኑን እናሳስባለን፡፡
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058-226-50-07 ደወለው መረጃ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን
ባሕር ዳር

