ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
18

የፍኖተ ሠላም ጠቅላላ ሆስፒታል ከወረቀት ነጻ የሆነ ህክምና ለመስጠት የፉል አዉቶ ሚሽን (ሙሉ ኔትወርኪግ) ሶፍት ዌር ለመግዛት ሶፍት ዌር አቅራቢዎችን በመጋበዝ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም፡-

  1. በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  1. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  2. የአንድ ጊዜ የግዥው መጠን ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  4. ተጫራቾች ከታወቀ የመንግስት ሆስፒታል ላይ የፉል አዉቶሜሽን (ሙሉ የኔትወርክ) ሥራ ለመስራታቸዉ የመልካም ሥራ አፈፃፀም ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  5. አሸናፊ የሚሆነዉ የሶፍት ዌር አቅራቢ ሶፍት ዌሩን ከሰራ (ከዘረጋ) በኋላ ለ3 ወር ስልጠና የሚሰጥ እና የሚአበቃ ይሆናል፡፡ አሸናፊዉ ለሰራተኛዉ ስልጠና ከሰጠ በኋላ ለ6 ወር ክትትል ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡
  6. ሸናፊው ተጫራች የሚሰራውን የሶፍትዌር አፕሊኬሽን (executable application)፣ የተቀናጀውን ዳታቤዝ (configured database) ለሆስፒታሉ የሚያስረክብ ይሆናል፡፡ እንዲሁም ሶፍትዌሩ ከሆስፒታሉ ነባር የጤና መድህን አስተዳደር ሲስተም እና ከሌሎች የሚመለከታቸው የላይዘን ሲስተሞች ጋር መገናኘት /መተሳሰር የሚችል መሆን አለበት፡፡
  7. ተጫራቾች ከዚህ ጋር በተያያዘው የዋጋ መሙያ መሰረት ዋጋ በመሙላት ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ አለባቸው፡፡
  8. በጨረታው አሸናፊ ሆኖ የሚመረጠው በቀረበው ዝርዝር መሠረት በእያንዳንዱ ሎት በጥቅል ድምር ዝቅተኛ ዋጋ ያቀረበው
    ድርጅት ሲሆን በጥቅል ድምር አሸናፊ ለሚለይባቸው ግዥዎች ለአንድም ግዥ ዋጋ አለመሙላት ከጨረታ ውድድር ውጭ ያደርጋል፡፡
  9. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የፋይናንስ ቡድን ቢሮ በመሄድ ለሰነዱ የመጫረቻ ሰነድ እያንዳንዳቸውን በብር 100 (አንድ መቶ ብር) ገዝተው መጫረት ይችላሉ፡፡ አሸናፊዉ ክፍያ የሚከፈለዉ ለ1 ዓመት የሚቆይ 5 በመቶ ሪቴሽን ተሰልቶ የሚቆረጥ እና ቀሪዉ ክፍያ በ3 ጊዜ የሚከፈል ይሆናል፡፡
  10. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ ወይም (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ዋስትና በፍ/ሠላም ጠቅላላ ሆስፒታል ስም ማስያዝ አለባቸው፡፡
  11. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሣቡን በአንድ ወይም በአንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች በማድረግ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በፍ/ሠላም ጠቅላላ ሆስፒታል በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ በ15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  12. ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በፍ/ሠላም ጠቅላላ ሆስፒታል በ3፡30 ታሽጎ በ4፡00 ይከፈታል፡፡ እለቱ ቅዳሜና እሁድ ወይም ህዝባዊ የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከረፋዱ 4፡00 ይከፈታል፡፡
  13. በጨረታው አሸናፊ የሆነ አቅራቢ የውል ማስከበሪያ 10 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ዋስትና ማስያዝ እና አገልግሎት ወጭ ችሎ ማስረከብ አለበት፡፡
  14. መስሪያ ቤቱ 20 በመቶ ከግዥዉ መጨመር ወይም መቀነስ ይችላል፡፡ የተሻለ አማራጭ ካገኘም ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  15. በማስታወቂያው ላይ ያልተገለፁ ነገሮች ቢኖሩም በግዥ መመሪያው መሰረት ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡
  16. ለበለጠ መረጃ በፋክስ ቁጥር 058 775 13 32 መላክ እንዲሁም በስልክ ቁጥር 058 775 00 16 /058 775 00 63 /058 775 10 16 በመደወል መረጃ መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የፍኖተ ሠላም ጠቅላላ ሆስፒታል

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here