የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ከዚህ በታች ያሉትን ክፍት የስራ መደቦች ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታውን ከሚያሟሉ ስራ ፈላጊዎች መካከል በጊዜአዊ የረዥም ጊዜ /በኮንትራት /ቅጥር አወዳድሮ በመቅጠር ማሰራት ይፈልጋል፡፡
| ተቁ | የሥራ መደቡ መጠሪያ | ደረጃ | የመ/መ/ቁ | ደመወዝ | ብዛት | ዳይሬክቶሬት | የሥራ ቦታ | አግባብ ያለው የትምህርት ዝግጅት | አግባብ ያለው የስራ ልምድ |
| 1 | ስርጭት ተቆጣጣሪ /ሱፐር ቫይዘር1/ | 13 | አሚ-1608 | በኮርፖሬሽኑ የደመወዝ ስኬል መሰረት | 01 | አዲስ አበባ ሚዲያ ቴክኖሎጂ | አዲስ አበባ | ኤሌክትሮኒክስ፣ ኮምፒውተርና ኤሌክትሮ ሜካኒካል፣ በብሮድካት ምህንድስና እንዲሁም በመረጃና ኮምንኬሽን ቴክኖሎጂ፣ በኤሌክትሮኒክስና ተግባቦት ቴክኖሎጂ፣ መልቲሚዲያና ኤሌክትሮኒክስ ኢኪውፕመንት ሰርቪሲን፣ በኤሌክተሮኒክስና ተግባቦት ቴክኖሎጂ ስራ አመራር ወይም ተዛማጅ የትምህርት መስክ የሰለጠነ | የመጀመሪያ ዲግሪና 5 ዓመት ወይም 2ኛ ዲግሪና 3 ዓመት አግባብነት ያለው የስራ ልምድ |
ማሳሰቢያ፡-
- የምዝገባ ቀን ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ5 ተከታታይ የስራ ቀናት ይሆናል፡፡
- አመልካቾች ለፈተና በሚቀርቡበት ጊዜ ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- አመልካቾች በእምነት ማጉደል በማጭበርበር ወይም በስርቆት ወንጀል ተከሰዉ ስልጣን ባለዉ አካል ተፈርዶባቸዉ የመቀጠር መብታቸዉን እንዲጠቀሙ ስልጣን ያለዉ ፍርድ ቤት የወሰነበትን ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- አመልካቾች ለፈተና በሚቀርቡበት ጊዜ ኦርጅናሉን የትምህርትና የስራ ልምድ ለተጠየቀበት መደብ ብቻ የስራ ልምዳቸውን መረጃ ኦርጅናል ይዞ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
- ከተጠቀሰዉ አግባብነት ያለው የትምህርት ዝግጅት እና የስራ ልምድ ውጭ ለምዝገባ የሚቀርቡ ሌሎች ማስረጃዎች ተቀባይነት አይኖራቸዉም፡፡
- አመልካቾች መልካም ስነ-ምግባር ያለው/ላት፡ ከማንኛውም ደባል ሱስ የፀዳ/ች፣ ጥሩ ስብዕና ያለው/ላት፡፡
- ተወዳዳሪዎች በተመዘገቡበት የስራ መደብ ለምን ተቀጥረው መስራት እንደፈለጉ በጽሁፍ ገልፀው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- አመልካቾች የሙያ ብቃት በሚያስፈልጋቸው የት/ት ዝግጅት የብቃት ማረጋገጫ በማስታወቂያው በተጠየቀው የት/ት ደረጃ ልክ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የሙያ ብቃት ምዘና ያልተጀመረባቸው የትምህርት መስኮች ከሚመለከተው ተቋም የሙያ ብቃት አለመጀመሩን ማስረጃ ካቀረቡ መመዝገብ ይችላሉ፡፡
- የኮንትራት ቅጥሩ ለ6 ወር ሆኖ እንደአስፈላጊነቱ በየ6 ወሩ ይታደሳል፡፡
- ተወዳድሮ ያለፈ የስራ ተያዥ/ዋስ/ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
- ፈተና የሚሰጥበት ቀንና ቦታ በሌላ ማስታወቂያ ይገለፃል፡፡
- አመልካቾች የምትመዘገቡበት ሊንክ በዌብሳይታችን ameco.et ማግኘት ትችላላችሁ ወይም
ይህ ሊንክ በመጫን ይመዝገቡ https://forms.gle/JpBsz2cQuii2oiS69 መመዝገብ የሚችሉ መሆኑን እናሳስባለን፡፡
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058 226 50 07 በመደወል መረጃ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን
ባህር ዳር

