ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
18

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ በምዕ/ጐጃም ዞን ገንዘብ መመሪያ የደም/ዙ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት በወረዳዉ ዉስጥ በሚገኙ ባለበጀት መ/ቤቶች ያሉ ሎት l. ቁርጥራጭ ብረታብረቶች፤ አገልግሎት የሰጡ የመኪና መለዋወጫወች እና የአገለገሉ የተለያዩ  የቢሮ ፕላንትና ማሽነሪ እና የተለያዩ የቢሮ መገልገያ ቁሳቁሶችን ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም፤

  1. ሎት l. ቁርጥራጭ ብረታብረቶችና የተሸከርካሪ መለዋወጫ ለሚሳተፉ፤
  • በዘርፉ የተሰማሩ እና በዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ አና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማቅረብ አለባቸው፡፡
  1. ያገለገሉ ንብረቶችን መግዛት የሚፈልጉ ግን ንግድ ፈቃድ ያለዉም ይሁን የሌለው ድርጅትና ግለሰብ መጫረት ይችላል፡፡
  2. በሽያጭ የሚወገዱ ቁርጥራጭ ብረቶችና ንብረቶችን መግዛት ወይም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ የንብረት ሽያጭ የጨረታ ሰነዱን ደም/ዙ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 6 ድረስ በመቅረብ 1ዐዐ (አንድ መቶ) ብር በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፡፡
  3. የጨረታ ማስታወቂያው በበኩር ጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር 15/አስራ አምስት/ ተከታታይ ቀን በአየር ላይ የሚቆይ ሲሆን በ16ኛው ቀን ከጥዋቱ 4፡ዐዐ ታሽጐ 4፡ዐዐ ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ይሆናል፡፡
  4. በተራ ቁጥር 4 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ቅዳሜ እና እሁድ ወይም የበዓላት ቀን ከሆነ በቀጣዩ ቀን በተመሳሳይ ስዓት የሚከፈት ይሆናል፡፡
  5. ተጫራቾች በንብረት ሽያጭ ጨረታው ላይ ለመሳተፍ የጨረታ ማስከበሪያ የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ በሲፒኦ ወይም ደም/ዙ/ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በደረሰኝ በማስያዝ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  6. በንብረት ሽያጭ ጨረታ የሚሳተፍ ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በጥንቃቄ በፖስታ በማሸግ  ስም፣ ፊርማ እና አድራሻ በማስቀመጥ ደም/ዙ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 6 በተዘጋጀው የጨረታ  ሳጥን ውስጥ ዘወትር በስራ ስዓት የጫራታ ሳጥኑ እስከሚዘጋበት ቀንና ስዓት ድረስ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል፡፡
  7. መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ የንበረት ሽያጭ ጫራታውን በሙሉም ይሁን በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  8. በንብረት ሽያጭ ጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ደም/ዙ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 6 በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር ዐ58773ዐ274 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

 

ደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

 

 

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here