ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
63

የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ በ2019 በጀት አመት የጽሕፈት መሳሪያ ግዥ እና የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ግዥ በአገር አቀፍ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡

የግዥው አይነት መለኪያ ብዛት
የጽህፈት መሳሪያ
ቀይ ቢክ እስክርቢቶ 1ኛው ፖኬት 2
ሰማያዊ ቢክ  እስክረቢቶ 1ኛው ፓኬት 88
ጥቁር ቢክ እስክርቢቶ 1ኛው ፓኬት 20
የኮምፒውተር ወረቀት A4 በደስታ 500
ካርቦን 3000H በደስጣ 5
እሁ ገም በቲዮብ 10
ትራንስፓረንሲ በደስታ 2
ሃርድ ከቨር በደስጣ 5
የማህተም ቀለም በቲዮብ 10
የፕሪንተር ቀለም 26A SW በቁጥር 70
የኮፒ ቀለምcannon IR2520/2525/2530 በቁጥር 10
መዝገብ የውጭ 25በ35 በቁጥር 30
ሸራ ፕላስተር በቁጥር 10
የእስቴፕለር ሽቦ ትንሹ በፓኮ 8
የእስቴፕለር ሽቦ ትልቁ በፓኮ 8
ካኪ ፖስታ A4 በደስታ 5
የእስቴፕለር መምቻ ትልቁ በቁጥር 10
የእስቴፕለር መምቻ ትንሹ በቁጥር 10
ማስታወሻ ደብተር ሲነር ላይን ባለ 100 ቅጠል በቁጥር 100
ካልኩሌተር ካሲዮ በቁጥር 6
ባለ ብረት አቃፊ ፋይል በቁጥር 200
ኮሬክሽን ፍሉድ አኳ በቲዮብ 12

 

የግዥው አይነት መለኪያ ብዛት
ኤሌክትሮኒክስ
ፍላሽ 64 ጅቢ በቁጥር 20
የፕሪንተር ኬብል ባለ3 ሜትር በሜትር 12
የኢንተርኔት ኬብል በሜትር 50
ዲቫይደር በቁጥር 10

 

 

ስለዚህም የሚከተሉትን ዝቅተኛ መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው እና ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  2. የግብር መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  3. የግዥው መጠን ብር 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ  ብር) እና በላይ  ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃ ፎቶ ከፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 300 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል ደ/ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ቢሮ 2ኛ ፎቅ የግዥና ፋይናንስ ቡድን ቢሮ ቁጥር 22 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  6. ስለ ዕቃው ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  7. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን ኦርጅናል በአንድ ፖስታ፣ ቅጅ በአንድ ፖስታ ውስጥ እና ሰነድ በማሸግ ደ/ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ 2ኛ ፎቅ ግዥ/ፋ/ን/አስ/ ቡድን ቢሮ ቁጥር 22 ውስጥ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15 ኛው ቀን 10፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለጽህፈት መሳሪያ ተወዳደሪዎች ብር 20,000 (ሃያ ሽህ) በባንክ በተመሰከረ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ አለባቸው፡፡ የጨረታ ማስከበሪያ ዋጋ ለ60 ቀናት የፀና መሆን ይኖርበታል፡፡
  9. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 22 ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ቆይቶ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ታሽጎ በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ይከፈታል፡፡ የመክፈቻ ቀኑ የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት ይሆናል፡፡
  10. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

የደ/ማርቆስ ከተማ አስ/ከ/መ/ል/ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here