የሐራጅ ጨረታ ማስታወቂያ

0
25

ፀደይ ባንክ (አ.ማ) ዘንገና ቅርንጫፍ ለአቶ አለኸኝ ጥላሁን እና ለወ/ሮ ማሪቱ መንግስቴ እና ቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ ቅርንጫፍ ለአቶ አለ አድማስ እና ወ/ሮ ብዙአየሁ ገነት ለሰጠው ብድር በዋስትና የያዛቸውንና በሰንጠረዥ ከዚህ በታች የተገለፁ መያዣዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና በተሻሻለው አዋጅ ቁጥር 216/92 በተሰጠው ስልጣን መሰረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡

የተበዳሪው ስም የመያዣ ሰጪ ስም የካርታ ቁጥር ቤቱ የሚገኝ በት ቦታ የቦታው ስፋት በካ/ሜ የንብረቱ አይነት አገልግሎት የጨረታ መነሻ ዋጋ የጨረታ ቀንና ሰዓት ጨረታ የወጣው
አለኸኝ ጥላሁን እና ማሪቱ መንግስቴ አለኸኝ ጥላሁን እና ማሪቱ መንግስቴ

 

 108/09  እንጅባራ ከተማ 01 ቀበሌ 200 ካ/ሜ  መኖሪያ 2,193,213.81 መስከረም 15/2019 ዓ/ም ከ3፡00-6፡00 ለመጀመሪያ ጊዜ
አለ አድማስ እና ብዙአየሁ ገነት

 

 አለ አድማስ እና ብዙአየሁ ገነት እና እመቤት አወቀ  

625/አ/4382 እና 402/በ/822

 

ዳንግላ ከተማ 04 ቀበሌ እና 05

 

150 ካ/ሜ እና 105 ካ/ሜ

 

መኖሪያ

952,334.72 እና 1,265,703.28  

መስከረም 15/2019 ዓ/ም ከ3፡00-6፡00

 

ለመጀመሪያ ጊዜ

 

 

ተጫራቾች ለጨረታ ከመቅረባቸው በፊት የሚከተሉትን ደንቦች መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡፡

  1. ተጫራቾች የቤቱን የጨረታ መነሻ ዋጋ ¼ኛውን (በጥሬ ገንዘብ ወይም (ሲፒኦ) በፀደይ ባንክ አ/ማ ስም በማሰራት ለጨረታ ማስከበሪያ በማስያዝ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡
  2. ተጫራቾች በሐራጅ ለመሳተፍ ሲመጡ ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ በጨረታው የሚሳተፈው በሕግ ሰውነት ያገኘ ሰው ከሆነ የፀደቀ የድርጅቱ መመሥረቻ ጽሑፍ ወይም መተዳደሪያ ደንብ፣ ሕጋዊ ሰውነት ያገኘበት የምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ ቃላ ጉባኤ ወይም ሕጋዊ የውክልና ሠነድ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  3. የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ የሚረጋገጠው የጨረታው ውጤት በሚመለከተው አካል ጸድቆ በባንኩ ደብዳቤ ሲሰጠው ይሆናል፡፡
  4. የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ ከባንኩ በደብዳቤ ከተገለፀለት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ በ15 ቀን ውስጥ አጠቃልሎ ከፍሎ በጨረታ ያሸነፈበትን ንብረት መረከብ ይኖርበታል፡፡ በእነዚህ ቀናት ውስጥ ካልከፈለ ጨረታው ተሰርዞ ለጨረታ ማስከበሪያ በሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል፡፡ በተጨማሪም ንብረቱ ድጋሚ ለሐራጅ ሲቀርብ ለሚታየው የዋጋ ልዩነት ይጠየቃል፡፡ ላላሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ሲፒኦ ይመለስላቸዋል፡፡
  5. የጨረታው አሸናፊ ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያያዙ ማንኛውንም ለመንግሥት የሚከፈሉ ክፍያዎች፣ ግብር፣ 15 በመቶ ተጨማሪ እሴት ታክስ የሚከፈል ከሆነ እንዲሁም ከስም ዝውውር ጋር የሚገናኙ ማንኛውንም ወጭዎች ይከፍላሉ፡፡
  6. ተጫራቾች ቤቱን በባንኩ አማካኝነት ጨረታው ከመከሄዱ በፊት አስቀድሞ ቀጠሮ በማስያዝ መጎብኘት ወይም ማየት ይችላሉ፡፡
  7. የጨረታው ቦታ በእንጅባራ ከተማ 01 ቀበሌ በሚገኘው የፀደይ ባንክ አ.ማ እንጅባራ ዲስትሪከት 3ኛ ፎቅ በሚገኘው አዳራሽ ውስጥ ነው፡፡
  8. ጨረታ የሚካሄደው መስከረም 15/2019 ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 5፡00 የተጫራቾች ምዝገባ ተካሂዶ ከረፋዱ 5፡00 እስከ 6፡00 ባለው ጊዜ ውስጥ በእንጅባራ ከተማ ፀደይ ባንክ እንጅባራ ዲስትሪክት ቢሮ ይካዳል፡፡
  9. የተጫራቾች ምዝገባ ከሐራጁ መዝጊያ ሰዓት 30 ደቂቃ በፊት ይጠናቀቃል፡፡
  10. ከፍተኛ ዋጋ የሰጠው ተጫራች የጨረታው አሸናፊ ነው የሚባለው ከባንኩ አሸናፊነቱን የሚገልጽ ደብደቤ በጽሁፍ ሲደርሰው ብቻ ነው፡፡
  11. ንብረቱ በገዥው ስም እንዲዞር ባንኩ ለሚመለከተው መንግስታዊ አካል ደብደቤ ይጽፋል፡፡
  12. ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  13. ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 058 227 07 08 /09 18 44 45 41 /09 18 80 27 26 በመደወል መረጃ መጠየቅ ይችላሉ፡፡

ፀደይ ባንክ (አ.ማ) እንጅባራ ዲስትሪክት

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here